የግርጌ ማስታወሻ
a በመጀመሪያዎቹ የሼክስፒር ሥራዎች ውስጥ የክርስቶፈር ማርሎው እጅ እንደነበረ ግልጽ ነው። ይሁን እንጂ ማርሎው በ1593 በ29 ዓመቱ በለንደን ከተማ ሞተ። አንዳንዶች ማርሎው በአንድ መጠጥ ቤት ውስጥ በተነሣ አምባ ጓሮ ምክንያት ሞቷል የተባለው በውሸት ሲሆን ወደ ኢጣሊያ ሄዶ የሥነ ጽሑፍ ሥራውን ቀጥሏል ይላሉ። ስለ መቀበሩም ሆነ ስለ ተደረገለት የቀብር ሥነ ሥርዓት የሚታወቅ ነገር የለም።