የግርጌ ማስታወሻ
a “ሕክምና ያልተደረገለት የስኳር በሽታ ስብ በደም ውስጥ በሚፈረካከስበት ጊዜ የሚከሰቱት ኬቶኖች እንዲከማቹ በማድረግ ደምኬቶናዊነት (ketosis) ያስከትላል፤ ይህ ደግሞ አሲዶሲስ (በደም ውስጥ የሚፈጠር የአሲድ ክምችት) እንዲሁም የማቅለሽለሽና የማስመለስ ችግር ያስከትላል። የካርቦሃይድሬትና የስብ የተዛባ ገንባፍራሽ ቅንባሮ (metabolism) መርዘኛ ውጤቶች መከማቸታቸውን ሲቀጥሉ ሕመምተኛው በስኳር በሽታ ሳቢያ በሚከሰት ኮማ ውስጥ ይገባል።”—ኢንሳይክለፒድያ ብሪታኒካ