የግርጌ ማስታወሻ
a ሐቀኛ የሆነ አንባቢ ፀሐይ በሰማይ ስለመቆሟ የሚናገረው መግለጫ ሁኔታው ሲከሰት የተመለከተ ሰው ከሰጠው ምሥክርነት አንጻር እንጂ ሳይንሳዊ ትንታኔ ለመስጠት የተነገረ አለመሆኑን መቀበል አያዳግተውም። የሥነ ፈለክ ተመራማሪዎችም ቢሆኑ ብዙውን ጊዜ ስለ ፀሐይ፣ ስለ ፕላኔቶችና ስለ ከዋክብት መውጣትና መጥለቅ ይናገራሉ። እንዲህ ሲሉ ግን እነዚህ የጠፈር አካላት ቃል በቃል በመሬት ዙሪያ ይዞራሉ ማለታቸው ሳይሆን በሰማይ ላይ የሚንቀሳቀሱ እንደሚመስሉ ማመልከታቸው ነው።