የግርጌ ማስታወሻ
a ኢየሱስ “የቄሣርን ለቄሣር” ስለመስጠት የሰጠው ምክር ግብር በመክፈል ብቻ የተወሰነ አይደለም። (ማቴዎስ 22:21) በሃይንሪክ ማየር የተዘጋጀው ክሪቲካል ኤንድ ኤክሰጀቲካል ሃንድቡክ ቱ ዘ ጎስፕል ኦቭ ማቲው የተባለው መጽሐፍ “የቄሣር ነገሮች . . . የግብርና የቀረጥ ግዴታዎችን ብቻ ሳይሆን ቄሣር በገዥነት ሥልጣኑ ምክንያት ያገኛቸውን መብቶችና ሥልጣኖች በሙሉ እንደሚያመለክት አድርገን መረዳት ይኖርብናል” ሲል ያብራራል።