የግርጌ ማስታወሻ
a የኅዳር 2004 ንቁ! መጽሔት “የወጣቶች ጥያቄ . . . እንደማፈቅረው እንዴት ብዬ ልገልጽለት እችላለሁ?” በሚለው ርዕስ ሥር በአንዳንድ አገሮች አንዲት ሴት አንድን ወንድ እንደምታፈቅረው መንገሯ እንደነውር እንደሚቆጠር ይገልጻል። መጽሐፍ ቅዱስ ሴት ስሜቷን ቀድማ መግለጽ የለባትም ባይልም ክርስቲያኖች ለሌሎች እንቅፋት እንዳይሆኑ ይመክራል። ስለዚህ በዚህ ረገድ ምን ቢያደርጉ እንደሚሻል የሚያስቡ እህቶች የአምላክን በረከት ማግኘት የሚፈልጉ ከሆነ የመጽሐፍ ቅዱስን ምክር መከተል ይገባቸዋል።—ማቴዎስ 18:6፤ ሮሜ 14:13፤ 1 ቆሮንቶስ 8:13