የግርጌ ማስታወሻ
f በሚውቴሽን ላይ የተደረጉት ሙከራዎች በተደጋጋሚ እንዳረጋገጡት በሚውቴሽን አማካኝነት አዳዲስ ባሕርያት ያላቸውን ዝርያዎች የማግኘቱ አጋጣሚ በጣም እየቀነሰ ሲሄድ ተመሳሳይ የባሕርይ ለውጥ ያደረጉ ዝርያዎችን የማግኘቱ አጋጣሚ ግን እየጨመረ መጥቷል። ሎኒግ ከዚህ ክስተት በመነሳት “ሎው ኦቭ ሪከረንት ቬሪዬሽን” (ተደጋግሞ የሚከሰት ልዩነት ደንብ) የሚባል ሕግ አውጥተዋል። በተጨማሪም ከዕፅዋት ሚውቴሽን ውጤቶች ውስጥ ለቀጣይ ምርምር ብቁ ሆነው የተገኙት ከ1 በመቶ ያነሱ ሲሆኑ ከእነዚህም መካከል የንግድ ጠቀሜታ እንዳላቸው የታመነባቸው ከ1 በመቶ ያነሱ ናቸው። እንስሳትን በሚውቴሽን በማዳቀል የተገኘውም ውጤት ከዚህ እጅግ የከፋ በመሆኑ ዘዴው ሥራ ላይ እንዳይውል ተደርጓል።