የግርጌ ማስታወሻ
a አንዳንዶች ለዚህ ሌላ ምክንያት ይሰጣሉ:- የግሪ ካውያን ፍልስፍና በአይሁዶች ላይ ተጽዕኖ ሳያሳድር አልቀረም ይላሉ። ለምሳሌ ያህል ኢየሱስ በኖረበት ዘመን አካባቢ በእስክንድርያ ይኖር የነበረው ፊሎ የተባለ አይሁዳዊ ፈላስፋ በመለኮታዊ መንፈስ ይመራል ብሎ በሚያስበው ፕላቶ የተባለ ግሪካዊ ፈላስፋ በእጅጉ ተነክቶ ነበር። ሌክሲኮን ደስ ጁደንቱምስ (የአይሁድ እምነት መዝገበ ቃላት) “ፊሎ” በሚለው ቃል ግርጌ “ፊሎ የግሪካውያንን (የፕላቶን) ፍልስፍና ቋንቋና አስተሳሰብ አምላክ ከገለጠው የአይሁድ እምነት ጋር አዋህዷል” ካለ በኋላ “በክርስትና አብያተ ክርስቲያናት አባቶች ላይም ጉልህ የሆነ ተጽዕኖ አሳድሯል” ይላል። ፊሎ አምላክ በቃላት ሊገለጽ የማይችል ስለሆነ በስምም ሊጠራ አይችልም የሚል እምነት ነበረው።