የግርጌ ማስታወሻ
a ዮሐንስ ከሞተ ከ60 ዓመታት ያህል ጊዜ በኋላ የ86 ዓመት ሽማግሌ የነበረው ፖሊካርፕ በኢየሱስ ላይ የነበረውን እምነት ለመካድ አሻፈረኝ በማለቱ በሰምርኔስ ከተማ በእሳት ተቃጥሎ ተገድሎአል። ይህ ድርጊት በተፈጸመበት ጊዜ የተጻፈ ነው የሚባለው የፖሊካርፕ ሰማዕትነት የተባለው መጽሐፍ እንደሚለው ፖሊካርፕ የተቃጠለበት እንጨት በሚሰበሰብበት ጊዜ “አይሁዳውያን እንደልማዳቸው በታላቅ ቅንዓት እንጨት በመሰብሰብ ሥራ ተካፍለው ነበር።” ፖሊካርፕ የተገደለው “በትልቁ የሰንበት ቀን” መሆኑ እንኳን በዚህ ሥራ እንዳይካፈሉ አላገዳቸውም።