የግርጌ ማስታወሻ
b በዮሐንስ ክፍል የሚታተመው መጠበቂያ ግንብ መጽሔት በዚህ አጋጣሚ መጠቀምና በተቻለ መጠን በስብከቱ ሥራ መካፈል በጣም አጣዳፊ መሆኑን ሲያስገነዝብ ቆይቶአል። ለምሳሌ ያህል፣ በጥር 1, 2004 መጠበቂያ ግንብ እትም ላይ “ሰው ሁሉ የይሖዋን ክብር ያውጅ” እና “‘ድምፃቸው በምድር ሁሉ ላይ ወጣ’” በሚሉ ርዕሶች የቀረቡትን ትምህርቶች ተመልከት። በሰኔ 1, 2004 እትም ላይ “ለአምላክ ክብር የሚሰጡ የተባረኩ ናቸው” በሚል ርዕስ በቀረበው ትምህርት ላይ ‘በተከፈተው በር’ ወደ ሙሉ ጊዜ አገልግሎት መግባት በጣም አስፈላጊ መሆኑ ተገልጿል። በ2005 በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ 1,093,552 የደረሰ ከፍተኛ የአቅኚዎች ቁጥር ሪፖርት ተደርጓል።