የግርጌ ማስታወሻ
b “ጥልቁ” (በግሪክኛ አቢሶስ፣ በዕብራይስጥ ቴሆሂም) ምንም ዓይነት ሥራ የማይኖርበትን ሥፍራ ያመለክታል። (ራእይ 9:2ን ተመልከት።) ይሁን እንጂ ቃል በቃል ሲወሰድ ሰፊውን ባሕር ሊያመለክት ይችላል። የዕብራይስጡ ቃል አብዛኛውን ጊዜ “ጥልቅ ባሕር” ተብሎ ይተረጎማል። (መዝሙር 71:20 NW፤ መዝሙር 106:9፤ ዮናስ 2:5 [2:4 የ1954 እትም]) ስለዚህ “ከጥልቁ የወጣው አውሬ” “ከባሕር ውስጥ ከወጣው አውሬ” ጋር አንድ ነው ሊባል ይችላል።—ራእይ 11:7፤ 13:1