የግርጌ ማስታወሻ
a “እጅግ አዘነ” ተብሎ የተተረጎመው የግሪክኛ ቃል ጥልቅ የሐዘን ስሜትን ከሚያመለክት ግስ (ኤምብሪማኦሜ) የተወሰደ ነው። አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ምሁር “እዚህ ላይ ቃሉ የሚያመለክተው ኢየሱስ የጠለቀ የሐዘን ስሜት ተሰምቶት ከልቡ እንደቃተተ ነው” ብለዋል። “ተረበሸ” ተብሎ የተተረጎመው የግሪክኛ ቃል መታወክን ከሚያመለክት ቃል (ታራሶ) የተወሰደ ነው። አንድ የመዝገበ ቃላት አዘጋጅ እንዳሉት ቃሉ “አንድ ሰው ውስጡ እንደተረበሸ እንዲሁም ከፍተኛ ሥቃይ ወይም ሐዘን እንደተሰማው” ይጠቁማል። “እንባውን አፈሰሰ” የሚለው አገላለጽ “ምንም ድምፅ ሳያሰሙ ማልቀስ” የሚል ትርጉም ካለው የግሪክኛ ግስ (ዳክሪኦ) የተወሰደ ነው።