የግርጌ ማስታወሻ
a ይህ ምዝገባ ለሮማ መንግሥት ግብር እንዲሰበሰብ የሚያስችል አመቺ ሁኔታ ፈጥሯል። ስለዚህም አውግስጦስ ሳያውቀው “አስገባሪውን የሚያሳልፍ በስፍራው ይነሣል” የሚለውን ትንቢት ፈጽሟል። ይኸው ትንቢት “የቃል ኪዳኑ አለቃ” ወይም መሲሑ በዚህ ንጉሥ ምትክ በሚነሣው ገዥ ዘመን ‘እንደሚሰበር’ ተንብዮአል። ኢየሱስ የተገደለው በአውግስጦስ ወራሽ በጢባርዮስ ዘመነ መንግሥት ነበር።— ዳንኤል 11:20–22