የግርጌ ማስታወሻ
a በሃይማኖት በተከፋፈለ ቤተሰብ ውስጥ የሚኖሩ ልጆችን በተመለከተ ዶክተር ስቲቨን ካር ሩበን፣ ሬይዚንግ ጁዊሽ ችልድረን ኢን ኤ ከንቴምፐራሪ ወርልድ በተባለው መጽሐፋቸው ላይ እንደሚከተለው ብለዋል፦ “ወላጆች እውነተኛ ማንነታቸውን ሲደብቁ፣ ግራ የሚያጋባና ሚስጥራዊ የሆነ ሕይወት ሲመሩ እንዲሁም ሃይማኖታዊ ጉዳዮችን ገሸሽ ሲያደርጉ ልጆች ግራ ይጋባሉ። ወላጆች ስለሚያምኑባቸው ነገሮች፣ ስለሚመሩባቸው ደንቦችና ስለሚያከብሯቸው በዓላት ግልጽና ሐቀኛ ሲሆኑ ልጆች ከሃይማኖታዊ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ የደኅንነት ስሜት ተሰምቷቸውና ለራሳቸው ጥሩ ግምት ኖሯቸው ያድጋሉ፤ ይህ ደግሞ በራሳቸው እንዲተማመኑና በኅብረተሰቡ ውስጥ ያላቸውን ቦታ እንዲገነዘቡ ትልቅ ሚና ይጫወታል።”