የግርጌ ማስታወሻ
b በአንዳንድ አገሮች ለአልኮል ሱሰኞችና ለቤተሰቦቻቸው የባለሙያ እርዳታ የሚሰጡ የሕክምና ማዕከሎች፣ ሆስፒታሎችና ከዚህ ሱስ ለመላቀቅ የሚረዱ ፕሮግራሞች አሉ። በእንዲህ ዓይነቱ እርዳታ መጠቀም አለመጠቀሙ የግል ውሳኔ ነው። የመጠበቂያ ግንብ ማኅበር የተሻለው ሕክምና ይኼኛው ነው ብሎ ሐሳብ አያቀርብም። ይሁን እንጂ አንድ ሰው እርዳታ ለማግኘት በሚጥርበት ጊዜ ቅዱስ ጽሑፋዊ የሆኑ መሠረታዊ ሥርዓቶችን የሚያስጥሱ ነገሮች እንዳይፈጽም መጠንቀቅ አለበት።