የግርጌ ማስታወሻ
a አንዳንድ ተቺዎች አንዳንድ የጥንት መጻሕፍት በብዕር ስሞች ይጻፉ እንደነበረ ሁሉ የዳንኤል መጽሐፍ ጸሐፊም ዳንኤል የሚለውን ስም የተጠቀመበት እንደ ብዕር ስም አድርጎ ነው በማለት የፈጠራ መጽሐፍ ነው የሚለውን ክስ ትንሽ ለማለዘብ ይሞክራሉ። ይሁን እንጂ የመጽሐፍ ቅዱስ ተቺ የሆኑት ፈርዲናንድ ሂትሲክ እንዲህ ብለዋል:- “የዳንኤል መጽሐፍ [ጸሐፊ] ሌላ ሰው ነው ካልን ጉዳዩ መልኩን ይቀይራል። እንደዚያ ከሆነ መጽሐፉ የፈጠራ መጽሐፍ ነው ማለት ነው፤ ጸሐፊው ለገዛ ጥቅማቸው አስቦም እንኳ ሊሆን ቢችል ዓላማው በጊዜው የነበሩትን አንባቢዎቹን ማታለል ነበር ማለት ይሆናል።”