የግርጌ ማስታወሻ
a ይህ መልአክ በስም ባይጠቀስም ስላየው ራእይ ዳንኤልን ይረዳው ዘንድ ለገብርኤል መመሪያ ሲሰጥ ድምፁ የተሰማው መልአክ ይመስላል። (ዳንኤል 8:2, 15, 16ን ከዳን 12:7, 8 ጋር አወዳድር።) ከዚህም በተጨማሪ ዳንኤል 10:13 ‘ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ’ የሆነው ሚካኤል ይህንን መልአክ ሊረዳው እንደመጣ ይገልጻል። በመሆኑም ይህ ስሙ ያልተገለጸው መልአክ ከገብርኤልና ከሚካኤል ጋር በቅርብ የመሥራት መብት ያለው መልአክ መሆን ይኖርበታል።