የግርጌ ማስታወሻ
a “ሰይጣን፣ ኢየሱስ የአምላክ ልጅ እንደሆነና አስቀድሞ በትንቢት በተነገረው መሠረት ራሱን እንደሚቀጠቅጠው (ዘፍ 3:15) በመገንዘብ ኢየሱስን ለማጥፋት ያልሸረበው ሴራ የለም። ይሁን እንጂ መልአኩ ገብርኤል ማርያም ኢየሱስን እንደምትጸንስ ባስታወቃት ጊዜ እንዲህ ብሏት ነበር:- ‘መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፣ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል፤ ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል።’ (ሉቃስ 1:35) ይሖዋ ልጁን ጠብቆታል። ኢየሱስን በሕፃንነቱ ለመግደል የተደረገው ሙከራ ሁሉ ሳይሳካ ቀርቷል።”—ቅዱሳን ጽሑፎችን ጠለቅ ብሎ ማስተዋል (እንግሊዝኛ) ጥራዝ 2 ገጽ 868፣ በይሖዋ ምሥክሮች የተዘጋጀ።