የግርጌ ማስታወሻ
a “ነገሮች ሁሉ የሚታደሱበት ዘመን” የጀመረው መሲሐዊው መንግሥት ተቋቁሞ የታማኙ ንጉሥ የዳዊት ወራሽ ዙፋን ላይ በተቀመጠበት ጊዜ ነው። ይሖዋ ለዳዊት፣ ዘሩ ለዘላለም እንደሚገዛ ቃል ገብቶለት ነበር። (መዝሙር 89:35-37) ይሁን እንጂ ኢየሩሳሌም በ607 ዓ.ዓ. በባቢሎን ከጠፋች በኋላ በአምላክ ዙፋን ላይ የነገሠ የዳዊት ዘር አልነበረም። ሆኖም የዳዊት ዘር ሆኖ በምድር ላይ የተወለደው ኢየሱስ በሰማይ ንጉሥ ሆኖ ሲሾም አስቀድሞ በትንቢት የተነገረለት የዙፋን ወራሽ ሆኗል።