የግርጌ ማስታወሻ
a በገሊላ ባሕር ላይ ድንገተኛ ማዕበል ብዙ ጊዜ ይነሳል። ይህ ባሕር በጣም ዝቅተኛ ቦታ ላይ (ከባሕር ወለል በታች 200 ሜትር ገደማ ዝቅ ብሎ) ስለሚገኝ ባሕሩ ላይ ያለው አየር በአካባቢው ካለው አየር ይበልጥ ሞቃታማ ነው፤ በዚህም የተነሳ በከባቢ አየር ውስጥ ነውጥ ይፈጠራል። በስተ ሰሜን በኩል ከሚገኘው የሄርሞን ተራራ ተነስተው ወደ ዮርዳኖስ ሸለቆ የሚነፍሱ ኃይለኛ ነፋሳት አሉ። ጸጥ ብሎ የነበረው የአየር ጠባይ ድንገት ተለውጦ ኃይለኛ ማዕበል ሊነሳ ይችላል።