የግርጌ ማስታወሻ
b ሚሽና እንደሚገልጸው ከሆነ በቤተ መቅደሱ የሚሸጡት ርግቦች ዋጋ እየተወደደ መምጣቱ ተቃውሞ አስነስቶ ነበር። ወዲያውኑ የርግቦቹ ዋጋ 99 በመቶ እንዲቀንስ ተደርጓል! በዚህ አትራፊ ንግድ ይበልጥ ይጠቀሙ የነበሩት እነማን ናቸው? አንዳንድ ታሪክ ጸሐፊዎች በቤተ መቅደሱ የሚካሄደውን ንግድ በአብዛኛው የተቆጣጠሩት የሊቀ ካህናቱ የሐና ቤተሰቦች እንደነበሩና ይህም ለቤተሰቡ ከፍተኛ ሀብት እንዳስገኘ ይናገራሉ።—ዮሐንስ 18:13