የግርጌ ማስታወሻ
b መጽሐፍ ቅዱስ በ2 ጢሞቴዎስ 4:2 ላይ ሽማግሌዎች አልፎ አልፎ ‘መውቀስ፣ መገሠጽ እንዲሁም አጥብቀው መምከር’ እንዳለባቸው ይናገራል። ‘አጥብቆ መምከር’ ተብሎ የተተረጎመው የግሪክኛ ቃል (ፓራካሌኦ) “ማበረታታት” ተብሎም ሊተረጎም ይችላል። ከዚህ ጋር ተዛማጅነት ያለው ፓራክሊቶስ የሚለው የግሪክኛ ቃል፣ ሕግ ነክ ለሆኑ ጉዳዮች ለአንድ ግለሰብ ጥብቅና የሚቆምን ሰው ሊያመለክት ይችላል። በመሆኑም ሽማግሌዎች ጠንከር ያለ ወቀሳ በሚሰጡበት ጊዜም እንኳ ግባቸው ግለሰቡን በመንፈሳዊ መርዳት ነው።