የግርጌ ማስታወሻ
a መጽሐፍ ቅዱስ በተደጋጋሚ ጊዜያት የትንሣኤ ተስፋን ከይሖዋ የማስታወስ ችሎታ ጋር አያይዞ ይገልጸዋል። ታማኙ የአምላክ አገልጋይ ኢዮብ ይሖዋን ‘ምነው ቀጠሮ ሰጥተህ ባስታወስከኝ!’ ብሎታል። (ኢዮብ 14:13) ኢየሱስ “በመታሰቢያ መቃብር ያሉ ሁሉ” ትንሣኤ እንደሚያገኙ ተናግሯል። ይሖዋ ከሞት ሊያስነሳቸው የሚፈልጋቸውን ሰዎች በሚገባ የሚያስታውሳቸው በመሆኑ ይህ አነጋገር ተገቢ ነው።—ዮሐንስ 5:28, 29