የግርጌ ማስታወሻ
b አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች ይህን ጥቅስ ሲተረጉሙ የአምላክን ሕዝብ የሚነካ የአምላክን ሳይሆን የራሱን ዓይን ወይም የእስራኤልን ሕዝብ ዓይን እንደሚነካ አድርገው ገልጸውታል። ይህ ስህተት የተፈጠረው በጥቅሱ ላይ የሰፈረው ሐሳብ አክብሮት የጎደለው እንደሆነ የተሰማቸው አንዳንድ ጸሐፊዎች ጥቅሱን በራሳቸው መንገድ ለማስተካከል በመሞከራቸው ነው። የወሰዱት የተሳሳተ እርምጃ የይሖዋ ጥልቅ የርኅራኄ ስሜት እንዲሰወር አድርጓል።