የግርጌ ማስታወሻ
a ከ455 ከክርስቶስ ልደት በፊት እስከ 1 ከክርስቶስ ልደት በፊት ድረስ 454 ዓመታት አሉ። ከ1 ከክርስቶስ ልደት በፊት እስከ 1 ከክርስቶስ ልደት በኋላ ድረስ አንድ ዓመት ነው። (ዜሮ የሚባል ዓመት የለም።) ከ1 ከክርስቶስ ልደት በኋላ እስከ 29 ከክርስቶስ ልደት በኋላ 28 ዓመት ነው። እነዚህን ሦስት አኃዞች ስንደምር 483 ዓመታት ይሆናሉ። ኢየሱስ ‘የተገደለው’ በ33 ከክርስቶስ ልደት በኋላ ማለትም በ70ኛው የዓመታት ሳምንት ነው። (ዳንኤል 9:24, 26) የዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል! የተባለውን መጽሐፍ ምዕራፍ 11 እና ቅዱሳን ጽሑፎችን ጠለቅ ብሎ ማስተዋል (እንግሊዝኛ) የተባለውን መጽሐፍ ጥራዝ 2 ከገጽ 899-901 ተመልከት። ሁለቱም ጽሑፎች የተዘጋጁት በይሖዋ ምሥክሮች ነው።