የግርጌ ማስታወሻ
a ኢየሱስ የተከተሉትን ሰዎች ሁሉ፣ ያላቸውን ንብረት በሙሉ ለሌሎች እንዲሰጡ አልጠየቃቸውም። ለሀብታም ሰው ወደ አምላክ መንግሥት መግባት አስቸጋሪ እንደሚሆንበት ቢናገርም “በአምላክ ዘንድ ሁሉ ነገር ይቻላል” ብሏል። (ማርቆስ 10:23, 27) ደግሞም ባለጸጋ የሆኑ ጥቂት ሰዎች የክርስቶስ ተከታዮች ሆነዋል። እነዚህ ሰዎች በክርስቲያን ጉባኤ ውስጥ ሀብትን በሚመለከት ቀጥተኛ ምክር የተሰጣቸው ቢሆንም ያላቸውን ሀብት ሁሉ ለድሆች እንዲሰጡ አልተጠየቁም።—1 ጢሞቴዎስ 6:17