የግርጌ ማስታወሻ
a የኬሚስትሪ ተማሪዎች እርሳስና ወርቅ ፔሬዲክ ቴብል በተባለው ሰንጠረዥ ላይ ተቀራራቢ በሆኑ ቦታዎች ላይ እንደሚገኙ ያውቃሉ። አንድ የእርሳስ አተም ከወርቅ አተም የሚለየው በኒውክለሱ ውስጥ ባሉት ሦስት ተጨማሪ ፕሮቶኖች ብቻ ነው። እንዲያውም በዘመናችን ያሉ የፊዚክስ ሊቃውንት በጣም ትንሽ መጠን ያለውን እርሳስ ወደ ወርቅ መለወጥ ችለዋል፤ ሆኖም ይህን ማድረግ ከፍተኛ ኃይል ስለሚጠይቅ ከወጪ አንጻር ሲታይ የሚያዋጣ ሆኖ አልተገኘም።