የግርጌ ማስታወሻ
a ሉቃስ በወንጌሉ ላይ ይህን ሰው “ክቡር ቴዎፍሎስ ሆይ” በማለት ጠርቶታል፤ በዚህም የተነሳ አንዳንዶች ቴዎፍሎስ በማኅበረሰቡ ዘንድ የተከበረ ቦታ ያለው ሰው እንደሆነና በወቅቱ ገና አማኝ እንዳልነበረ ይገምታሉ። (ሉቃስ 1:3) በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ላይ ግን ሉቃስ ይህን ሰው “ቴዎፍሎስ ሆይ” በማለት ብቻ ጠርቶታል። አንዳንድ ምሁራን ቴዎፍሎስ የሉቃስ ወንጌልን ካነበበ በኋላ አማኝ እንደሆነ ይገልጻሉ፤ ሉቃስ የሐዋርያት ሥራን ሲጽፍ የአክብሮት መግለጫ ያልተጠቀመው እንደ መንፈሳዊ ወንድሙ አድርጎ ስለቆጠረው እንደሆነ ይናገራሉ።