የግርጌ ማስታወሻ
b ከሁኔታው መረዳት እንደሚቻለው በዚያ ወቅት አዳዲስ ደቀ መዛሙርት በመንፈስ ቅዱስ የሚቀቡት ወይም መንፈስ ቅዱስን የሚቀበሉት በአብዛኛው በሚጠመቁበት ጊዜ ነበር። ይህም ከኢየሱስ ጋር በሰማይ ነገሥታትና ካህናት ሆነው የመግዛት ተስፋ እንዲኖራቸው ያደርጋል። (2 ቆሮ. 1:21, 22፤ ራእይ 5:9, 10፤ 20:6) በዚህ ጊዜ ግን አዲሶቹ ደቀ መዛሙርት በተጠመቁበት ወቅት በመንፈስ ቅዱስ አልተቀቡም። አዲሶቹ ክርስቲያኖች መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉትም ሆነ ከዚያ ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ተአምራዊ ስጦታዎች ያገኙት ጴጥሮስና ዮሐንስ እጃቸውን ከጫኑባቸው በኋላ ነበር።