የግርጌ ማስታወሻ a አንዳንድ አይሁዳውያን፣ ቆዳ ፋቂዎችን ይንቁ ነበር፤ ምክንያቱም በዚህ ሙያ የተሰማራ ሰው የእንስሳት ቆዳና በድን መንካቱ አይቀርም፤ ከዚህም ሌላ ቆዳውን ሲያዘጋጅ እንደ ውሻ እዳሪ የመሳሰሉ ነገሮችን ይጠቀም ነበር። ቆዳ ፋቂዎች ወደ ቤተ መቅደሱ እንዲገቡ አይፈቀድላቸውም፤ የሚሠሩበት ቦታም ከከተማ ቢያንስ 50 ክንድ ወይም 20 ሜትር ገደማ መራቅ ነበረበት። የስምዖን ቤት “ባሕሩ አጠገብ” የሆነበት አንዱ ምክንያት ይህ ሊሆን ይችላል።—ሥራ 10:6