የግርጌ ማስታወሻ
b ጸሐፊ የሆኑ አንድ ሐኪም እንደገለጹት ጆሴፈስም ሆነ ሉቃስ የገለጿቸው የበሽታ ምልክቶች በጥገኛ ትላትሎች ምክንያት የሚከሰቱ ሳይሆኑ አይቀሩም፤ ትላትሎቹ የአንጀት ቱቦን በመዝጋት ለሞት ሊዳርጉ ይችላሉ። አንዳንድ ጊዜ ሕመምተኛው ሲያስመልስ እነዚህ ትላትሎች ይወጣሉ፤ ወይም ሰውየው ሲሞት ከሰውነቱ እየተርመሰመሱ ይወጣሉ። አንድ የማመሣከሪያ ጽሑፍ እንዳለው “የሕክምና ባለሙያ የሆነው ሉቃስ ሁኔታውን ቁልጭ አድርጎ የገለጸበት መንገድ [የሄሮድስ] አሟሟት ምን ያህል ዘግናኝ እንደነበር በግልጽ ያስረዳል።”