የግርጌ ማስታወሻ
b ያዕቆብ ከሙሴ መጻሕፍት ላይም ማጣቀሱ ጥበብ የሚንጸባረቅበት ነው። እነዚህ መጻሕፍት ሕጉን ብቻ ሳይሆን ከሕጉ በፊት አምላክ ከሰዎች ጋር ስለነበረው ግንኙነት የሚገልጹ ዘገባዎችን ይዘዋል፤ ዘገባዎቹ፣ የሙሴ ሕግ ከመሰጠቱ በፊት የአምላክ ፈቃድ ምን እንደነበረ ይጠቁማሉ። ለምሳሌ ያህል፣ አምላክ ስለ ደም፣ ስለ ምንዝርና ስለ ጣዖት አምልኮ ያለው አመለካከት በዘፍጥረት መጽሐፍ ውስጥ በግልጽ ሰፍሯል። (ዘፍ. 9:3, 4፤ 20:2-9፤ 35:2, 4) በመሆኑም ይሖዋ አይሁዳዊ፣ አሕዛብ ሳይል መላው የሰው ዘር ሊጠብቃቸው የሚገቡ መሠረታዊ ሥርዓቶችን ሰጥቷል።