የግርጌ ማስታወሻ
b ሐዋርያው ጳውሎስ ከጥቂት ዓመታት በኋላ ለዕብራውያን ክርስቲያኖች ደብዳቤ ጻፈ፤ በደብዳቤው ላይ የአዲሱን ቃል ኪዳን ብልጫ አስረግጦ ተናግሯል። አዲሱ ቃል ኪዳን አሮጌውን የሚተካ እንደሆነ በግልጽ አስረድቷል። ጳውሎስ፣ እነዚያ ክርስቲያኖች ለአይሁዳውያን ተቃዋሚዎቻቸው መልስ ለመስጠት የሚያስችሏቸው አሳማኝ ማስረጃዎች አቅርቧል፤ ከዚህም ሌላ ጳውሎስ ያቀረባቸው ጠንካራ ነጥቦች ለሙሴ ሕግ አላስፈላጊ ትኩረት የሚሰጡ ክርስቲያኖችን እምነት አጠናክረው መሆን አለበት።—ዕብ. 8:7-13