የግርጌ ማስታወሻ
a ጳውሎስ፣ አናሲሞስን እሱ ጋር ሊያስቀረው ፈልጎ ነበር። ይሁን እንጂ እንዲህ ቢያደርግ የሮምን ሕግ መጣስ ይሆንበታል፤ የአናሲሞስ ጌታ የሆነውን ፊልሞና የተባለውን ክርስቲያን መብትም ይጋፋል። በመሆኑም አናሲሞስ፣ ጳውሎስ ለፊልሞና የጻፈውን ደብዳቤ ይዞ ወደ ጌታው ተመልሷል፤ ጳውሎስ በደብዳቤው ላይ ፊልሞና፣ ባሪያውን እንደ መንፈሳዊ ወንድም ቆጥሮ በደግነት እንዲቀበለው አበረታቶታል።—ፊልሞና 13-19