የግርጌ ማስታወሻ
e የሚውቴሽን ሙከራዎች ብዙ ጊዜ እንዳረጋገጡት በሚውቴሽን አማካኝነት አዳዲስ ባሕርያት ያላቸውን ዝርያዎች የማግኘቱ አጋጣሚ እየቀነሰ የሚሄድ ሲሆን ከዚያ በኋላ በተደጋጋሚ ሙከራ ቢደረግም የሚገኙት ዝርያዎች ቀደም ሲል ከተገኙት የተለዩ አይሆኑም። በተጨማሪም ከዕፅዋት ሚውቴሽን ውጤቶች ውስጥ ለቀጣይ ምርምር የተመረጡት ከ1 በመቶ ያነሱ ሲሆኑ ከእነዚህ መካከል ለንግድ መዋል እንደሚችሉ የታመነባቸውም ከ1 በመቶ ያነሱ ናቸው። ይሁን እንጂ ሙሉ በሙሉ አዲስ የሆነ አንድም ዝርያ እስከ ዛሬ አልተፈጠረም። እንስሳትን በሚውቴሽን በማዳቀል የተገኘውም ውጤት ዕፅዋትን በማዳቀል ከተገኘው ውጤት የከፋ በመሆኑ ዘዴው ጨርሶ ሥራ ላይ እንዳይውል ተደርጓል።