የግርጌ ማስታወሻ
b ኒው ሳይንቲስት የተሰኘው መጽሔትም ሆነ ባቴስትና ሮዝ ይህን የገለጹት የዝግመተ ለውጥ ጽንሰ ሐሳብ ስህተት ነው ለማለት ፈልገው እንዳልሆነ ልብ ሊባል ይገባል። ከዚህ ይልቅ ሁለቱም ሊያስገነዝቡ የፈለጉት የዳርዊን ጽንሰ ሐሳብ ዋነኛ ክፍል የሆነው የሕይወት ዛፍ በማስረጃ የተደገፈ አለመሆኑን ነው። እንደነዚህ ያሉ ሳይንቲስቶች ስለ ዝግመተ ለውጥ ሌላ ማብራሪያ ለማግኘት አሁንም ጥረት በማድረግ ላይ ናቸው።