የግርጌ ማስታወሻ
e ቀዳማዊ ጠረክሲስ ስሜቱ የሚለዋወጥ ግልፍተኛ ሰው በመሆኑ ይታወቃል። ግሪካዊው የታሪክ ምሁር ሄሮዶተስ፣ ጠረክሲስ ከግሪክ ጋር ስላደረገው ጦርነት በጻፈው ታሪክ ላይ ስለ ንጉሡ ባሕርይ የሚገልጹ አንዳንድ ምሳሌዎችን ጠቅሷል። ንጉሡ በሄሌስፖንት ወሽመጥ ላይ መርከቦችን በመደርደር ድልድይ እንዲሠራ ትእዛዝ ሰጥቶ ነበር። ድልድዩን ማዕበል ባፈረሰው ጊዜ ጠረክሲስ መሃንዲሶቹ አንገታቸው እንዲቀላ ያዘዘ ከመሆኑም ሌላ ከፍ ባለ ድምፅ እርግማን በሚነበብበት ጊዜ አገልጋዮቹ ውኃውን በመግረፍ ሄሌስፖንትን “እንዲቀጡ” መመሪያ ሰጥቷል። ይህ ጦርነት በተካሄደበት ጊዜ አንድ ባለጸጋ ሰው ልጁ ከውትድርና ግዳጅ ነፃ እንዲሆን ሲለምነው ጠረክሲስ ልጁ ለሁለት እንዲቆረጥ ያዘዘ ከመሆኑም ሌላ መቀጣጫ እንዲሆን አስከሬኑ ሌሎች በሚያዩት ስፍራ እንዲቀመጥ አድርጓል።