የግርጌ ማስታወሻ
a ‘ዓለም ሲመሠረት’ የሚለው አገላለጽ ዘር መዝራትን ይኸውም መዋለድን ያመለክታል፤ በመሆኑም ይህ አገላለጽ መጀመሪያ ከተወለደው የሰው ልጅ ጋር የተያያዘ መሆን አለበት። ታዲያ ኢየሱስ የአዳምና የሔዋን የመጀመሪያ ልጅ የሆነውን ቃየንን ሳይሆን አቤልን ‘ከዓለም መመሥረት’ ጋር አያይዞ የጠቀሰው ለምንድን ነው? ከሁኔታዎች መመልከት እንደሚቻለው ቃየን ያደረገው ውሳኔና የፈጸመው ድርጊት በይሖዋ አምላክ ላይ ሆን ብሎ ከማመፅ አይተናነስም። በመሆኑም እንደ ወላጆቹ ሁሉ ቃየንም የኃጢአት ይቅርታም ሆነ ትንሣኤ የሚያገኝ አይመስልም።