የግርጌ ማስታወሻ
c በዕብራይስጥ ቅዱሳን መጻሕፍት ውስጥ “ሰይጣን” የሚለው ቃል አንድን አካል ለማመልከት 18 ጊዜ ተሠርቶበታል። በክርስቲያን ግሪክኛ ቅዱሳን መጻሕፍት ውስጥ ግን “ሰይጣን” የሚለው ቃል ከ30 ጊዜ በላይ ይገኛል። የዕብራይስጥ ቅዱሳን መጻሕፍት ለሰይጣን አላስፈላጊ ትኩረት ከመስጠት ይልቅ የመሲሑን ማንነት ጎላ አድርገው መግለጻቸው የተገባ ነው። መሲሑ በመጣ ጊዜ የሰይጣንን ማንነት ሙሉ በሙሉ አጋልጧል፤ የክርስቲያን ግሪክኛ ቅዱሳን መጻሕፍት የያዙት ዘገባ ለዚህ ማስረጃ ይሆናል።