የግርጌ ማስታወሻ
b ሥራው በኃላፊነት ለተሰጣቸው ሁሉ (እንግሊዝኛ) የተሰኘ በ1919 የታተመ ቡክሌት እንዲህ ይላል፦ “ወርቃማው ዘመን የተባለውን መጽሔት የምናሰራጨው የመንግሥቱን መልእክት ከቤት ወደ ቤት ለማድረስ ነው። . . . በእያንዳንዱ ቤት መልእክቱን ከተናገርን በኋላ የቤቱ ባለቤቶች የመጽሔት ኮንትራት ገቡም አልገቡ ወርቃማው ዘመን የተባለውን መጽሔት እንሰጣቸዋለን።” ከዚያ በኋላ ለብዙ ዓመታት ወንድሞች፣ ወርቃማው ዘመን እና መጠበቂያ ግንብ የተባሉትን መጽሔቶች ኮንትራት እንዲያስገቡ ይበረታቱ ነበር። ከየካቲት 1, 1940 አንስቶ የይሖዋ ሕዝቦች የእነዚህን መጽሔቶች ነጠላ ቅጂዎች እንዲያበረክቱና ያበረከቱትን ቁጥር ሪፖርት እንዲያደርጉ ማበረታቻ ይሰጣቸው ጀመር።