የግርጌ ማስታወሻ
a ከሌሎች አገሮች ወደ ቤተ መቅደሱ የሚመጡ አይሁዳውያን የቤተ መቅደሱን ዓመታዊ ግብር የሚከፍሉት በአካባቢው በሚሠራበት ገንዘብ መሆን ነበረበት፤ በመሆኑም ገንዘብ መንዛሪዎች የተወሰነ ዋጋ በማስከፈል ገንዘባቸውን ይቀይሩላቸው ነበር። በተጨማሪም ሰዎቹ መሥዋዕት ለማቅረብ እንስሳት መግዛት ያስፈልጋቸው ይሆናል። ኢየሱስ ነጋዴዎቹን “ዘራፊዎች” በማለት የጠራቸው ለሚሰጡት አገልግሎት በጣም የተጋነነ ዋጋ ይጠይቁ ስለነበር ሳይሆን አይቀርም።