የግርጌ ማስታወሻ
a ወልድ እንዴት ማስተማር እንዳለበት አብ እንዳሠለጠነው በምን እናውቃለን? እስቲ ይህን አስብ፦ ኢየሱስ በሚያስተምርበት ወቅት በርካታ ምሳሌዎችን መጠቀሙ እሱ ከመወለዱ ከብዙ ዘመናት በፊት የተጻፈ ትንቢት እንዲፈጸም አድርጓል። (መዝ. 78:2፤ ማቴ. 13:34, 35) ከዚህ መመልከት እንደምንችለው ይህንን ትንቢት ያስነገረው ይሖዋ፣ ልጁ በምሳሌዎች ተጠቅሞ እንደሚያስተምር ከረጅም ጊዜ በፊት ያውቅ ነበር። —2 ጢሞ. 3:16, 17