የግርጌ ማስታወሻ
a በተጨማሪም ግዞተኞቹ አይሁዳውያን ከትውልድ አገራቸው መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ አንጻር ይህ ወንዝ እውነተኛ ወንዝ እንዳልሆነ ሳይገነዘቡ አይቀሩም፤ ምክንያቱም ወንዙ የሚፈሰው በትልቅ ተራራ ላይ ከሚገኝ ቤተ መቅደስ ተነስቶ ነው፤ ይህ ቤተ መቅደስ ደግሞ በተጠቀሰው ቦታ ላይ አይገኝም። ከዚህም ሌላ ራእዩ፣ ወንዙ ምንም ነገር ሳያግደው በቀጥታ ወደ ሙት ባሕር እንደፈሰሰ የሚጠቁም ሊሆን ይችላል፤ ይህም ቢሆን ከአካባቢው መልክዓ ምድር አንጻር ሊሆን የሚችል ነገር አይደለም።