የግርጌ ማስታወሻ
a ስማቸው በራሱ የሚያስተላልፈው ትርጉም አለ። ኦሆላ የሚለው ስም “የእሷ [የአምልኮ] ድንኳን” የሚል ትርጉም አለው፤ ይህም እስራኤል በኢየሩሳሌም በሚገኘው የይሖዋ ቤተ መቅደስ ከመጠቀም ይልቅ የራሷን የአምልኮ ማዕከሎች ማቋቋሟን የሚያመለክት ስያሜ ሳይሆን አይቀርም። ኦሆሊባ ማለት ደግሞ “[የአምልኮ] ድንኳኔ በእሷ ውስጥ ነው” ማለት ነው። ኢየሩሳሌም የይሖዋ የአምልኮ ቤት የሚገኝባት ከተማ ነበረች።