የግርጌ ማስታወሻ
a “ቀራጮች በፍልስጥኤም ይኖሩ በነበሩ የአይሁድ ሕዝብ በተለይ ይጠሉ የነበሩት በተለያዩ ምክንያቶች ነበር፦ (1) የእስራኤልን ምድር ለያዘው የውጭ ኃይል ገንዘብ ይሰበስቡ ነበር፤ በዚህም በተዘዋዋሪ ለዚህ ግፍ ድጋፋቸውን ይሰጡ ነበር፤ (2) በደንታ ቢስነታቸው ምክንያት መጥፎ ስም ነበራቸው፤ የገዛ ሕዝባቸው በሆኑ በሌሎች ሰዎች ሐብት የሚበለጽጉ ነበሩ፤ እንዲሁም (3) ሥራቸው ከአሕዛብ ጋር ዘወትር እንዲገናኙ የሚያደርጋቸው ነበር፤ ይህም በሥነ ስርዓት እንዲረክሱ ያደርጋቸዋል። ለቀራጮች ሰዎች የነበራቸው ንቀት በአዲስ ኪዳን ውስጥም ሆነ በራባይ ጽሑፎች ውስጥ ተጽፎ ይገኛል። . . . [በራባይ ጽሑፍ] መሠረት ጥላቻው ለቀራጩ ቤተሰብም የሚተርፍ ነበር።”—ዘ ኢንተርናሽናል ባይብል ኢንሳይክሎፔዲያ