የግርጌ ማስታወሻ
a ጳውሎስ በግዝረት ጉዳይ ላይ ምላሽ የሰጠባቸውን ሁለት መንገዶች አወዳድር። መገረዝ ከንቱ መሆኑን ቢያውቅም በእናቱ በኩል አይሁዳዊ የነበረውን ጢሞቴዎስን ገርዞታል። (1 ቆሮንቶስ 7:19፤ ሥራ 16:3) ቲቶን ግን ከይሁዲነት ጠበቆች ጋር በነበረው ክርክር ምክንያት ሕግ ግዴታ ያለመሆኑን ለማሳየት እንዳይገረዝ አድርጐታል። (ገላትያ 2:3) ቲቶ ግሪካዊ ነበር። ስለዚህ እንደ ጢሞቴዎስ እንዲገረዝ የሚያደርገው ምክንያት አልነበረውም። ከአሕዛብ የነበረ እንደመሆኑ ቢገረዝ ኖሮ “ክርስቶስ ምንም አይጠቅመውም” ነበር።—ገላትያ 5:2-4