የግርጌ ማስታወሻ
a ኢየሱስና ያዕቆብ ሁለቱም በምድር ላይ ለ“ሦስት ዓመት ተኩል” ዝናብ እንዳልዘነበ ተናግረዋል። ሆኖም ኤልያስ ድርቁ ማክተሙን ለመንገር ወደ አክአብ ፊት የቀረበው “በሦስተኛው ዓመት” እንደሆነ የተነገረው ኤልያስ ድርቅ እንደሚሆን ካስታወቀበት ጊዜ ጀምሮ ሲቆጠር እንደሆነ አያጠራጥርም። በመሆኑም ኤልያስ መጀመሪያ በአክአብ ፊት የቀረበው ከረዥም ዝናብ አልባ ደረቅ ወቅት በኋላ መሆን አለበት።—ሉቃስ 4:25፤ ያዕቆብ 5:17፤ 1 ነገሥት 18:1