የግርጌ ማስታወሻ
a ምንም እንኳ የጥንታዊቷ ግሪክ ጥበበኞች ብዙ ፍልስፍና ነክ ክርክርና ምርምር ቢያደርጉም ለእውነተኛ ተስፋ ምክንያት የሚሆናቸው ምንም ነገር እንዳላገኙ ጽሑፎቻቸው ያሳያሉ። ጄ አር ኤስ ስቴረትና ሳሙኤል አንገስ የተባሉት ፕሮፌሰሮች “ከግሪካውያን ሥነ ጽሑፎች የበለጠ የሕይወትን አሳዛኝነት፣ የፍቅርን ዘላቂ አለመሆን፣ የተስፋን አታላይነትና የሞትን ጭካኔ የሚመለከቱ አሳዛኝ ምሬቶች የተገለጸበት ሥነ ጽሑፍ የለም” በማለት ያስገነዝባሉ።—የፈንክና የዋግናልስ አዲስ “መደበኛ” የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፣ 1936፣ ገጽ 313