የግርጌ ማስታወሻ
a በቅርቡ ጥናት የሚያካሂዱ ሰዎች በቴሌቪዥን ላይ በግልጽ በሚታይ ወንጀልና በወጣቶች በሚፈጸሙ የዓመፅ ድርጊቶች መካከል ግንኙነት እንዳለ ተገንዝበዋል። ከፍተኛ ወንጀል የተስፋፋባቸው አካባቢዎችና የተበታተኑ ቤተሰቦችም ለጸረ ማኅበራዊ ጠባዮች መንስኤዎች ናቸው። በናዚ ጀርመን የማያቋርጥ የዘረኝነት ፕሮፓጋንዳ አንዳንድ ሰዎች በአይሁድና በባሪያዎች ላይ የተፈጸመው ጭካኔ ተገቢ እንደሆነ እንዲሰማቸው፣ አልፎ ተርፎም እንዲኩራሩበት አድርጓቸዋል።