የግርጌ ማስታወሻ
b ከብዙ ጸሎትና ከብዙ የአምላክ ቃል ጥናት በኋላ ጆሴፍ ራዘርፎርድ በጀርመን ላሉት ወንድሞች ምን ብሎ መልስ እንደሚሰጣቸው በግልጽ ተገነዘበ። ምን ማድረግ እንዳለባቸውና እንደሌለባቸው የሚነግራቸው እርሱ አለመሆኑን አወቀ። በስብሰባና በመመስከር ረገድ ምን ማድረግ እንዳለባቸው በግልጽ የሚነግራቸው የአምላክ ቃል ነው። ስለዚህ የጀርመን ወንድሞች በድብቅ ለመሥራት ተገደዱ። አንድ ላይ መሰብሰብንና ስለ ይሖዋ ስምና ስለ መንግሥቱ መመስከርን በሚመለከት የይሖዋን ትእዛዝ መታዘዛቸውን ቀጠሉ።