የግርጌ ማስታወሻ
a ኢየሱስ ፍጹም አካሉ በእንጨት ላይ ከተሰቀለ ብዙም ሳይቆይ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ መሞቱ ችሎ የጸናው መከራ የቱን ያህል ከባድ እንደነበረ ያሳያል። ከጎኑ የተሰቀሉትን ክፉ አድራጊዎች ሞት ለማፋጠን ግን እግራቸውን መስበር አስፈልጎ ነበር። (ዮሐንስ 19:31–33) ኢየሱስ ከመሰቀሉ በፊት እንቅልፍ ባይኑ ሳይዞር ባሳለፈው ሌሊት የደረሰበትን ዓይነት አእምሮአዊና አካላዊ ሥቃይ በእነርሱ ላይ አልደረሰም። የደረሰበት ሥቃይ በጣም ከባድ ከመሆኑ የተነሳ የሚሰቀልበትን የመከራ እንጨት እንኳን መሸከም እስከሚያቅተው ድረስ አድክሞት የነበረ ይመስላል። — ማርቆስ 15:15, 21